መዝሙር 80:4-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤በሕዝብህ ጸሎት ላይ ቍጣህ የሚነደው፣እስከ መቼ ድረስ ነው?

5. የእንባ እንጀራ አበላሃቸው፤ስፍር የሞላ እንባም አጠጣሃቸው።

6. ለጎረቤቶቻችን የጠብ ምክንያት አደረግኸን፤ጠላቶቻችንም ተሣሣቁብን።

7. የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ መልሰን፤እንድንም ዘንድ፣ፊትህን አብራልን።

መዝሙር 80