5. በጫካ መካከል ዛፎችን ለመቍረጥ፣መጥረቢያ የሚያነሣ ሰው መሰሉ።
6. በእደ ጥበብ ያጌጠውን ሥራ ሁሉ፣በመጥረቢያና በመዶሻ ሰባበሩት።
7. መቅደስህን አቃጥለው አወደሙት፤የስምህንም ማደሪያ አረከሱ።
8. በልባቸውም፣ “ፈጽሞ እንጨቍናቸዋለን” አሉ፤እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ የተመለከበትን ስፍራ ሁሉ አቃጠሉ።
9. የምናየው ምልክት የለም፤ከእንግዲህ የሚነሣ አንድም ነቢይ የለም፤ይህ እስከ መቼ እንደሚቀጥል የሚያውቅ በእኛ ዘንድ የለም።
10. አምላክ ሆይ፤ ጠላት የሚያሾፈው እስከ መቼ ነው?ባላንጣስ ለዘላለም በስምህ ያላግጣልን?
11. እጅህን ለምን ትሰበስባለህ?ቀኝ እጅህን ለምን በብብትህ ሥር ታቆያለህ?