መዝሙር 65:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ በጽዮን ለአንተ ውዳሴ ይገባል፤ለአንተ የተሳልነውን እንፈጽማለን።

2. ጸሎትን የምትሰማ ሆይ፤የሰው ልጆች ሁሉ ወደ አንተ ይመጣሉ።

3. ኀጢአት ባጥለቀለቀን ጊዜ፣አንተ መተላለፋችንን ይቅር አልህ።

4. አንተ የመረጥኸው፣ ወደ ራስህ ያቀረብኸው፣በአደባባይህም ያኖርኸው ምስጉን ነው!ከተቀደሰው መቅደስህ፣ከቤትህም በረከት እንረካለን።

መዝሙር 65