መዝሙር 63:1-3 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤አንተን ከልብ እሻለሁ፤ ውሃ በሌለበት፣በደረቅና በተራቈተ ምድር፣ነፍሴ አንተን ተጠማች፤ሥጋዬም አንተን ናፈቀች።

2. ስለዚህ በመቅደስ ውስጥ አየሁህ፤ኀይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ።

3. ምሕረትህ ከሕይወት ይበልጣልና፤ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

መዝሙር 63