መዝሙር 41:2-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፤ በሕይወትም ያኖረዋል፤በምድርም ላይ ይባርከዋል፤ለጠላቶቹም ምኞትም አሳልፎ አይሰጠውም።

3. ታሞ ባለበት ዐልጋ ላይ እግዚአብሔር ይንከባከበዋል፤በበሽታውም ጊዜ መኝታውን ያነጥፍለታል።

4. እኔም፣ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረት አድርግልኝ፤አንተን በድያለሁና ነፍሴን ፈውሳት” አልሁ።

5. ጠላቶቼ በክፋት በመናገር፣ “የሚሞተው መቼ ነው? ስሙስየሚደመሰሰው ምን ቀን ነው?” ይላሉ።

6. ሊጠይቀኝ የሚመጣ ቢኖር፣በልቡ ስድብ እያጠራቀመ፣ ከዐንገት በላይ ይናገራል፤ወጥቶም ወሬ ይነዛል።

7. ጠላቶቼ ሁሉ ግንባር ፈጥረው ይንሾካሾኩብኛል፤እንዲህ እያሉም፣የከፋ ነገር በላዬ ያውጠነጥናሉ፤

መዝሙር 41