መዝሙር 34:8-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፤እርሱን መጠጊያ የሚያደርግ ምንኛ ቡሩክ ነው!

9. እናንተ ቅዱሳኑ፤ እግዚአብሔርን ፍሩት፤እርሱን የሚፈሩት አንዳች አያጡምና።

10. አንበሶች ሊያጡ፣ ሊራቡም ይችላሉ፤ እግዚአብሔርን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም።

11. ልጆቼ ሆይ፣ ኑ፤ ስሙኝ፤ እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።

12. ሕይወትን የሚወድ፣በጎውንም ያይ ዘንድ ዕድሜን የሚመኝ ማን ነው?

13. አንደበትህን ከክፉ ነገር ከልክል፤ከንፈርህንም ከሽንገላ ጠብቅ።

14. ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ፤ሰላምን ፈልጋት፤ ተከተላትም።

15. የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው፤ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ክፍት ናቸው።

16. መታሰቢያቸውን ከምድር ለማጥፋት፣ የእግዚአብሔር ፊት በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።

17. ጻድቃን ሲጮኹ፣ እግዚአብሔር ይሰማቸዋል፤ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል።

መዝሙር 34