1. እግዚአብሔር ሆይ፤ በአንተ ተተግኛለሁ፤እንግዲህ ዕፍረት ከቶ አይድረስብኝ፤በጽድቅህም ታደገኝ።
2. ጆሮህን ወደ እኔ መልሰህ ስማኝ፤ፈጥነህ አድነኝ፤መጠጊያ ዐለት ሁነኝ፤ታድነኝም ዘንድ ምሽግ ሁነኝ።
3. አንተ ዐለቴና መጠጊያዬ ነህና፣ስለ ስምህ ስትል ምራኝ፤መንገዱንም ጠቍመኝ።
4. አንተ መጠጊያዬ ነህና፣በስውር ከተዘረጋብኝ ወጥመድ አውጣኝ።
5. መንፈሴን በእጅህ ዐደራ እሰጣለሁ፤ እግዚአብሔር የእውነት አምላክ ሆይ፤አንተ ተቤዠኝ።