መዝሙር 119:96-103 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

96. ለፍጹምነት ሁሉ ዳርቻ እንዳለው አየሁ፤ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው።

97. አቤቱ፤ ሕግህን ምንኛ ወደድሁ!ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ።

98. ትእዛዛትህ ምንጊዜም ስለማይለዩኝ፣ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረጉኝ።

99. ምስክርነትህን አሰላስላለሁና፣ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የላቀ አስተዋይ ልብ አገኘሁ።

100. መመሪያህን ተከትዬ እሄዳለሁና፣ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋይ ሆንሁ።

101. ቃልህን እጠብቅ ዘንድ፣እግሬን ከክፉ መንገድ ሁሉ ከለከልሁ።

102. አንተው ራስህ አስተምረኸኛልና፣ከድንጋጌህ ዘወር አላልሁም።

103. ቃልህ ለምላሴ ምንኛ ጣፋጭ ነው!ለአፌም ከማር ወለላ ይልቅ ጣዕም አለው።

መዝሙር 119