86. ትእዛዛትህ ሁሉ አስተማማኝ ናቸው፤ሰዎች ያለ ምክንያት አሳደውኛልና ርዳኝ።
87. ከምድር ላይ ሊያስወግዱኝ ጥቂት ቀራቸው፤እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም።
88. እንደ ምሕረትህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ፤እኔም የአፍህን ምስክርነት እጠብቃለሁ።
89. እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃልህ በሰማይ፣ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።
90. ታማኝነትህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ሁሉ ይኖራል፤ምድርን መሠረትሃት፤ እርሷም ጸንታ ትኖራለች።
91. ሁሉም አገልጋይህ ነውና፣በሕግህ መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ ጸንተው ይኖራሉ።