53. ሕግህን ከተዉ ክፉዎች የተነሣ፣ቍጣ ወረረኝ።
54. በእንግድነቴ አገር፣ሥርዐትህ መዝሙሬ ናት።
55. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህን በሌሊት ዐስባለሁ፤ሕግህንም እጠብቃለሁ።
56. ሥርዐትህን እከተላለሁ፤ይህችም ተግባሬ ሆነች።
57. እግዚአብሔር ዕድል ፈንታዬ ነው፤ቃልህን ለመታዘዝ ቈርጫለሁ።
58. በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ።
59. መንገዴን ቃኘሁ፤አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ።
60. ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም።