152. ለዘላለም እንደ መሠረትሃቸው፣ከጥንት ምስክርነትህ ተረድቻለሁ።
153. ሕግህን አልረሳሁምና፣ ሥቃዬን ተመልከት፤ ታደገኝም።
154. ተሟገትልኝ፤ አድነኝም፤እንደ ቃልህም ሕያው አድርገኝ።
155. ሥርዐትህን ስለማይሹ፣ድነት ከክፉዎች የራቀ ነው።
156. እግዚአብሔር ሆይ፤ ርኅራኄህ ታላቅ ነው፤እንደ ሕግህ ሕያው አድርገኝ።
157. የሚያሳድዱኝ ጠላቶቼ ብዙዎች ናቸው፤እኔ ግን ከምስክርህ ዘወር አላልሁም።