15. ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ።
16. በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤ቃልህንም አልዘነጋም።
17. ሕያው እንድሆን፣ ቃልህንም እንድጠብቅ፣ለአገልጋይህ መልካም አድርግ።
18. ከሕግህ ድንቅ ነገርን እንዳይ፣ዐይኖቼን ክፈት።
19. እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝ፤ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር።
20. ዘወትር ደንብህን በመናፈቅ፣ነፍሴ እጅግ ዛለች።
21. ከትእዛዛትህ የሳቱትን፣እብሪተኞችንና ርጉሞችን ትገሥጻለህ።
22. ምስክርነትህን ጠብቄአለሁና፣ስድብንና ንቀትን ከእኔ አርቅ።