ሉቃስ 1:52-59 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

52. ገዢዎችን ከዙፋናቸው አውርዶአቸዋል፤ትሑታንን ግን ከፍ ከፍ አድርጎአቸዋል፤

53. የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአቸዋል፤ሀብታሞችን ግን ባዶአቸውን ሰዶአቸዋል፤

54. ምሕረቱን በማስታወስ፣ ባሪያውንእስራኤልን ረድቶአል፤

55. ይህም ለአባቶቻችን እንደ ተናገረ፣ለአብርሃምና ለዘሩ ያለውን ለዘላለም ለመጠበቅ ነው።”

56. ማርያምም ሦስት ወር ያህል ኤልሳቤጥ ዘንድ ከቈየች በኋላ ወደ ቤቷ ተመለሰች።

57. የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ቀን ደረሰ፤ ወንድ ልጅም ወለደች።

58. ጎረቤቶቿና ዘመ ዶቿም ጌታ ታላቅ ምሕረት እንዳደረገላት ሰሙ፤ የደስታዋም ተካፋዮች ሆኑ።

59. በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፤ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ፈለጉ፤

ሉቃስ 1