ሆሴዕ 2:10-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. አሁንም በውሽሞቿ ፊት፣ነውሯን እገልጣለሁ፤ከእጄም የሚያድናት የለም።

11. የደስታ በዓሎቿን ሁሉ፣የዓመት በዓሎቿንና፣ የወር መባቻዎቿንሰንበቶቿንና የተመረጡ በዓሎቿን ሁሉ አስቀራለሁ።

12. ከውሽሞቼ የተቀበልሁት ዋጋ ነው የምትለውን፤የወይን ተክሎቿንና የበለስ ዛፎቿን አጠፋለሁ፤ጫካ አደርገዋለሁ፤የዱር አራዊትም ይበሉታል።

13. ለበኣል አማልክት፣ ዕጣን ስላጠነችባቸው ቀናትእቀጣታለሁ፤በጌጣ ጌጥና በቀለበቶች ራሷን አስጊጣለች፤ውሽሞቿንም ተከትላ ሄዳለች፤እኔን ግን ረስታለች”ይላል እግዚአብሔር።

14. “ስለዚህ እነሆ፤ አባብላታለሁ፤ወደ ምድረ በዳም እወስዳታለሁ፤በፍቅር ቃል አነጋግራታለሁ።

15. በዚያም የወይን ተክሏን እመልስላታለሁ፤የአኮርንም ሸለቆ የተስፋ በር እንዲሆናት አደርጋለሁ።በዚያም ከግብፅ እንደ ወጣችበት ቀን፣እንደ ልጅነቷም ጊዜ ትዘምራለች።

ሆሴዕ 2