1. የነቢያት ማኅበር ኤልሳዕን እንዲህ አሉት፤ “እነሆ፣ በፊትህ የምንቀመጥበት ስፍራ ጠቦናል፤
2. ስለዚህ ወደ ዮርዳኖስ ሄደን፣ እያንዳንዳችን ምሰሶ ቈርጠን እናምጣ፣ በዚያም የምንቀመጥበትን መኖሪያ እንሥራ።”እርሱም፣ “ይሁን ሂዱ” አላቸው።
3. ከመካከላቸውም አንዱ፣ “አንተስ ከአገልጋዮችህ ጋር አትመጣምን?” አለው።ኤልሳዕም፣ “እሺ እሄዳለሁ” አለ፤
4. አብሮአቸውም ሄደ። ወደ ዮርዳኖስም ሄደው ዛፎች መቊረጥ ጀመሩ።