2. ይሁዳ ከወንድሞቹ ይልቅ ብርቱ ነበረ፤ ገዥ የወጣው ከእርሱ ቢሆንም፣ የብኵርና መብቱ የተላለፈው ለዮሴፍ ነበረ።
3. የእስራኤል የበኵር ልጅ የሮቤል ወንዶች ልጆች፤ሄኖኅ፣ ፋሉሶ፣ አስሮን፣ ከርሚ።
4. የኢዩኤል ዘሮችልጁ ሸማያ፣ ልጁ ጎግ፣ ልጁሰሜኢ፣
5. ልጁ ሚካ፣ልጁ ራያ፣ ልጁ ቢኤል፣
6. የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር ማርኮ የወሰደው ልጁ ብኤራ።
7. የቤተ ሰቡ የዘር ትውልድ በየጐሣ በየጐሣው ሲቈጠር እንደሚከተለው ነው፤የጐሣ አለቃ የሆነው ኢዮኤል፣ ዘካርያስ፣
8. የኢዮኤል ልጅ፣ የሽማዕ ልጅ፣ የዖዛዝ ልጅ ቤላ፣ እነዚህ ከአሮዔር እስከ ናባውና እስከ በኣልሜዎን ድረስ በሚገኘው ምድር ላይ ሰፈሩ።