1 ዜና መዋዕል 4:25-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. ሰሎም የሳኡል ልጅ ነው፤ መብሳም የሰሎም ልጅ ነው፤ማስማዕ ደግሞ የመብሳም ልጅ ነው።

26. የማስማዕ ዘሮችልጁ ሃሙኤል፣ ልጁ ዘኩር፣ ልጁ ሰሜኢ።

27. ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም።

28. የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፤ ቤርሳቤህ፣ ሞላደ፣ ሐጻርሹዓል፣

29. ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣

30. ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣

31. ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው።

32. በአካባቢያቸው የሚገኙት መንደሮች ደግሞ ኤጣም፣ ዓይን፣ ሬሞን፣ ቶኬን፣ ዓሻን የተባሉ አምስት ከተሞች ናቸው፤

1 ዜና መዋዕል 4