23. ሰዎቹ በነጣዒምና በጋዴራ የሚቀመጡ ሸክላ ሠሪዎች ነበሩ፤ በዚያም በመቀመጥ ለንጉሡ ሸክላ ይሠሩ ነበር።
24. የስምዖን ዘሮች፤ነሙኤል፣ ያሚን፣ ያሪን፣ ዛራ፣ ሳኡል፤
25. ሰሎም የሳኡል ልጅ ነው፤ መብሳም የሰሎም ልጅ ነው፤ማስማዕ ደግሞ የመብሳም ልጅ ነው።
26. የማስማዕ ዘሮችልጁ ሃሙኤል፣ ልጁ ዘኩር፣ ልጁ ሰሜኢ።
27. ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም።
28. የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፤ ቤርሳቤህ፣ ሞላደ፣ ሐጻርሹዓል፣
29. ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣
30. ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣
31. ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው።
32. በአካባቢያቸው የሚገኙት መንደሮች ደግሞ ኤጣም፣ ዓይን፣ ሬሞን፣ ቶኬን፣ ዓሻን የተባሉ አምስት ከተሞች ናቸው፤
33. በእነዚህም ከተሞች ዙሪያ እስከ በኣል የሚዘልቁ መንደሮች ነበሩ፤ መኖሪያቸው በዚሁ ሲሆን፣ የትውልድ መዝገብም አላቸው።
34. ሞሾባብ፣ የምሌክ፣ የአሜስያስ ልጅ ኢዮስያስ፣
35. ኢዮኤል፣ የዮሺብያ ልጅ፣ የሠራያ ልጅ፣ የዓሢኤል ልጅ ኢዩ
36. እንዲሁም ኤልዩዔናይ፣ ያዕቆባ፣ የሾሐያ፣ ዓሣያ፣ ዓዲዔል፣ ዩሲምኤል፣ በናያስ፣