6. የሌዋዊው የናትናኤል ልጅ ጸሓፊው ሸማያ በንጉሡና በሹማምቱ፣ በካህኑ በሳዶቅ፣ በአብያታር ልጅ በአቤሜሌክ እንዲሁም በካህናቱና በሌዋውያኑ ቤተ ሰብ አለቆች ፊት ስማቸውን ጻፈ፤ የጻፈውም አንዱን ቤተ ሰብ ከአልዓዛር ሌላውን ደግሞ ከኢታምር በመውሰድ ነው፤
7. የመጀመሪያው ዕጣ ለዮአሪብ፣ሁለተኛውም ዕጣ ለዮዳሄ ወጣ፤
8. ሦስተኛው ለካሪም፣አራተኛው ለሥዖሪም፣
9. አምስተኛው ለመልክያ፣ስድስተኛው ለሚያሚን፣
10. ሰባተኛው ለአቆስ፣ስምንተኛው ለአብያ፣
11. ዘጠነኛው ለኢያሱ፣ዐሥረኛው ለሴኬንያ፣
12. ዐሥራ አንደኛው ለኤሊያሴብ፣ዐሥራ ሁለተኛው ለያቂም፣
13. ዐሥራ ሦስተኛው ለኦፖ፣ዐሥራ አራተኛው ለየሼብአብ፣
14. ዐሥራ አምስተኛው ለቢልጋ፣ዐሥራ ስድስተኛው ለኢሜር፣
15. ዐሥራ ሰባተኛው ለኤዚር፣ዐሥራ ስምንተኛው ለሃፊጼጽ፣
16. ዐሥራ ዘጠነኛው ለፈታያ፣ሃያኛው ለኤዜቄል፣
17. ሃያ አንደኛው ለያኪን፣ሃያ ሁለተኛው ለጋሙል፣
18. ሃያ ሦስተኛው ለድላያ፣ሃያ አራተኛ ለመዓዝያ ወጣ።