1 ዜና መዋዕል 2:5-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. የፋሬስ ወንዶች ልጆች፤ኤስሮም፣ ሐሙል።

6. የዛራ ወንዶች ልጆች፤ዘምሪ፣ ኤታን፣ ሄማን፣ ከልኮል፣ ዳራ፤ ባጠቃላይ አምስት ናቸው።

7. የከርሚ ወንድ ልጅ አካን፤እርሱም ፈጽሞ መደምሰስ የነበረበትን ነገር ሰርቆ በእስራኤል ላይ ጥፋት እንዲመጣ ያደረገ ነው።

8. የኤታን ወንድ ልጅ፤አዛርያ።

9. የኤስሮም ወንዶች ልጆች፤ይረሕምኤል፣ አራም፣ ካሌብ።

10. አራም አሚናዳብን ወለደ፤አሚናዳብም የይሁዳ ሕዝብ መሪ የሆነውን ነአሶንን ወለደ፤

11. ነአሶን ሰልሞንን ወለደ፤ ሰልሞን ቦዔዝን ወለደ።

12. ቦዔዝ ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድ እሴይን ወለደ።

13. የእሴይ ወንዶች ልጆች፤የበኵር ልጁ ኤልያብ፣ ሁለተኛ ልጁ አሚናዳብ፣ ሦስተኛ ልጁ ሣማ፣

14. አራተኛ ልጁ ናትናኤል፣ አምስተኛ ልጁ ራዳይ፣

15. ስድስተኛ ልጁ አሳም፣ ሰባተኛ ልጁ ዳዊት።

1 ዜና መዋዕል 2