1 ዜና መዋዕል 2:40-48 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

40. ኤልዓሣ ሲስማይን ወለደ፤ሲስማይ ሰሎምን ወለደ፤

41. ሰሎም የቃምያን ወለደ፤የቃምያም ኤሊሳማን ወለደ።

42. የይረሕምኤል ወንድም የካሌብ ወንዶች ልጆች፤የበኵር ልጁ ሞሳ ሲሆን፣ እርሱም ዚፍን ወለደ፤ ዚፍም መሪሳን ወለደ፤ መሪሳም ኬብሮንን ወለደ።

43. የኬብሮን ወንዶች ልጆች፤ቆሬ፣ ተፉዋ፣ ሬቄም፣ ሽማዕ።

44. ሽማዕ ረሐምን ወለደ፤ ረሐምም ዮርቅዓምን ወለደ። ሬቄም ሸማይን ወለደ፤

45. ሸማይም ማዖንን ወለደ፤ ማዖንም ቤት ጹርን ወለደ።

46. የካሌብ ቁባት ዔፉ ሐራንን፣ ሞዳን፣ ጋዜዝን ወለደች። ሐራንም ጋዜዝን ወለደ።

47. የያህዳይ ወንዶች ልጆች፤ሬጌም፣ ኢዮታም፣ ጌሻን፣ ፋሌጥ፣ ዔፋ፣ ሸዓፍ።

48. የካሌብ ቁባት ማዕካ ሼቤርን፣ ቲርሐናን ወለደችለት።

1 ዜና መዋዕል 2