24. ኤስሮም በካሌብ ኤፍራታ ከሞተ በኋላ፣ ሚስቱ አቢያ የቴቁሔን አባት አሽሑርን ወለደችለት።
25. የኤስሮም የበኵር ልጅ የይረሕምኤል ወንዶች ልጆች፤የበኵር ልጁ ራም፣ ቡናህ፣ ኦሬን፣ ኦጼም፣ አኪያ።
26. ይረሕምኤል ዓጣራ የተባለች ሌላ ሚስት ነበረችው፤ እርሷም የኦናምን እናት ነበረች።
27. የይረሕምኤል የበኵር ልጁ የራም ወንዶች፤መዓስ፣ ያሚን፣ ዔቄር።
28. የኦናም ወንዶች ልጆች፤ሸማይና ያዳ።የሸማይ ወንዶች ልጆች፤ናዳብና አቢሱር።
29. የአቢሱር ሚስት አቢካኢል ትባላለች፤ እርሷም አሕባንንና ሞሊድ የተባሉ ልጆች ወለደችለት።
30. የናባድ ወንዶች ልጆች፤ሴሌድ፣ አፋይም፤ ሴሌድ ወንድ ልጅ ሳይወልድ ሞተ።
31. የአፋይም ወንድ ልጅ፤ይሽዒ። ይሽዒም ሶሳን ወለደ።ሶሳን አሕላይን ወለደ።
32. የሸማይ ወንድም የያዳ ወንዶች ልጆች፤ ዬቴር፣ ዮናታን፤ ዬቴርም ልጅ ሳይወልድ ሞተ።
33. የዮናታን ወንዶች ልጆች፤ፌሌት፣ ዛዛ።እነዚህ የይረሕምኤል ዘሮች ነበሩ።
34. ሶሳን ሴቶች ልጆች እንጂ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም።እርሱም ኢዮሄል የተባለ ግብፃዊ አገልጋይ ነበረው።
35. ሶሳን ልጁን ለአገልጋዩ ለኢዮሄል ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠው፤ እርሷም ዓታይ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደችለት።