1 ዜና መዋዕል 2:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የእስራኤል ወንዶች ልጆች እነዚህ ነበሩ፤ ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፣

2. ዳን፣ ዮሴፍ፣ ብንያም፣ ንፍታሌም፣ ጋድ፣ አሴር።

3. የይሁዳ ወንዶች ልጆች፤ዔር፣ አውናን፣ ሴሎም፤ እነዚህን ሦስቱን ከከነዓናዊት ሚስቱ ከሴዋ ወለደ። የበኵር ልጁ ዔር በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሰው ሆነ፤ እግዚአብሔርም ቀሠፈው።

4. የልጁም ሚስት የነበረችው ትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደችለት፤ ይሁዳም ባጠቃላይ አምስት ወንዶች ልጆች ነበሩት።

5. የፋሬስ ወንዶች ልጆች፤ኤስሮም፣ ሐሙል።

6. የዛራ ወንዶች ልጆች፤ዘምሪ፣ ኤታን፣ ሄማን፣ ከልኮል፣ ዳራ፤ ባጠቃላይ አምስት ናቸው።

7. የከርሚ ወንድ ልጅ አካን፤እርሱም ፈጽሞ መደምሰስ የነበረበትን ነገር ሰርቆ በእስራኤል ላይ ጥፋት እንዲመጣ ያደረገ ነው።

8. የኤታን ወንድ ልጅ፤አዛርያ።

1 ዜና መዋዕል 2