1 ተሰሎንቄ 5:21-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. ሁሉን ነገር ፈትኑ፤ መልካም የሆነውን ያዙ፤

22. ከማናቸውም ዐይነት ክፉ ነገር ራቁ።

23. የሰላም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ።

24. የጠራችሁ የታመነ ነው፤ እርሱም ያደርገዋል።

25. ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ።

1 ተሰሎንቄ 5