13. ስለ ሥራቸውም በፍቅር እጅግ አክብሯቸው። እርስ በርሳችሁም በሰላም ኑሩ።
14. ወንድሞች ሆይ፤ ይህን እንመክራችኋለን፤ ሥራ ፈቶችን ገሥጿቸው፤ ፈሪዎችን አደፋፍሯቸው፤ ደካሞችን እርዷቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።
15. ማንም በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፤ ነገር ግን እርስ በርሳችሁም ሆነ ለሌሎች ሰዎች ሁል ጊዜ መልካም የሆነውን ነገር ለማድረግ ተጣጣሩ።
16. ሁል ጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
17. ሳታቋርጡ ጸልዩ፤
18. በማናቸውም ሁኔታ አመስግኑ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ለእናንተ ይህ ነውና።
19. የመንፈስን እሳት አታዳፍኑ፤
20. ትንቢትን አትናቁ።
21. ሁሉን ነገር ፈትኑ፤ መልካም የሆነውን ያዙ፤
22. ከማናቸውም ዐይነት ክፉ ነገር ራቁ።
23. የሰላም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁ፣ ነፍሳችሁና ሥጋችሁ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ።
24. የጠራችሁ የታመነ ነው፤ እርሱም ያደርገዋል።
25. ወንድሞች ሆይ፤ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ።
26. ወንድሞችን ሁሉ በተቀደሰ አሳሳም ሰላም በሏቸው።
27. ይህ መልእክት ለወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ ዐደራ እላችኋለሁ።
28. የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።